Welcome to Lideta Subcity Good Governance, Compliance and Grievance Office!       እንኳን ወደ ልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት በሰላም መጡ!       Baga gara Waajjira Bulchiinsa Gaarii, Komii fi Ol iyyannoo Kutaa Magaalaa Lidataatti dhuftan!!

የልደታ ክፍለ ከተማ
መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት

የልደታ ክፍለ ከተማ
መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት

የልደታ ክፍለ ከተማ
መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት

የልደታ ክፍለ ከተማ
መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት

የልደታ ክፍለ ከተማ
መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት

የልደታ ክፍለ ከተማ
መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት


የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት

በመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን እና ለሚያጋጥም ቅሬታና አቤቱታ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት፣ ስህተቶችን ለማረምና አገልግሎት አሰጣጡን ውጤታማ ለማድረግ፤ በየደረጃው ያለ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ኃላፊ እና ሠራተኛ ለህብረተሰቡ በሚሰጡት አገልግሎት አስተዳደራዊ ጥፋትና በደል እንዳይፈፀሙ መከላከልና ተፈጽሞ ሲገኝ ተጠያቂ ለማድረግ እና በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀ የመስሪያ ቤት ኃላፊና ሠራተኛ በማፍራት ውጤታማ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር ማስቻል ነው፡፡

አላማውን መሰረት በማድረግ በክፍለ ከተማችን በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ቁጥር እና የአገልግሎት ፍላጎት በመንግስት ተቋማት የሚሰጡ የአገልግሎት ዓይነቶችና ብዛት እንዲጨምር በማድረጉ ተቋማት የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ከነዋሪው ሕዝብ ፍላጎት ጋር ለማጣጣም በየጊዜው አዳዲስ ማሻሻያዎች እየተደረገ ይገኛል፡፡ ... ተጨማሪ ያንብቡ

አቶ ይልማ ተረፈ , የልደታ መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ኃላፊ
image description

ዋና ዋና አገልግሎቶች

የቅሬታና አቤቱታ ምርመራ አገልግሎት
የወሳኔ አፈጻጸም ክትትል አገልግሎት
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መለየትና መፍታት፤ ድጋፍና ክትትል ማድረግ
የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራርና ድጋፍ አገልግሎት
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለከተማ አስተዳደር መልካም አስተዳደር ቅሬትና አቤቱታ ፅህፈት ቤት የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።

ተግባራትን በተቀናጀ ሁኔታ በመፈፀም የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመፍታት ተጠቃሚነቱን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ ተችሏል:- አቶ አሰፋ ቶላ በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት አመት የ6 ወራት የመልካም አስተዳደር ስራዎች እና የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር አፈፃፀም ተገመገመ፡፡ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው የተቋማት ተወካዮች በተገኙበት አስተዳደሩ በበጀት አመቱ 6 ወራት ያከናወናቸው የመልካም አስተዳደር ችግር አፈታት አፈፃፀም ተገምግሟል፡፡ መድረኩን የመሩት የክፍለ ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅ/ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አሰፋ ቶላ ሲሆኑ አብዛኞቹ ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ሂደት የተገኘባቸው መሆኑን ጠቅሰው በሁሉም ዘርፍ የታቀዱ ተግባራት ስኬታማ ሆነው እንዲጠናቀቁ ህብረተሰቡን በማሳተፍ መረባረብ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ መሠረታዊ የሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በቅንጅት እየፈታን የማህበረሰባችንን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ እየሰራን ነው ያሉት አቶ አሰፋ አስተዳደሩ ህገ-ወጥነትንና ብልሹ አሰራርን በመታገል በነዋሪው ዘንድ ፍትሃዊ የሆነ ተጠቃሚነት እንዲኖርም ይሰራል ብለዋል። አቶ አሰፋ አያይዘው ተግባራትን በተቀናጀ ሁኔታ በመፈፀም የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመፍታት ተጠቃሚነቱን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል። የዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጢቂ ድሪባ በበኩላቸው በተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር እና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄዎች መነሻ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ ያሉበት ደረጃ ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀው ቀሪ ስራዎችን በታቀደላቸው የጊዜ ገደብ መሰረት በማጠናቀቅ መረባረብ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ይልማ ተረፈ በአፈፃፀም መድረኩ ላይ እንዳሉት በባለፋት 6 ወራት የተለዩትን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመርህ እና በአሰራር በመፍታት የአስተዳደሩን ለህዝብ ጥያቄ ቅድሚያ ሰጥቶ የመመለስ መርህ በሚገባ አሳክተናል ብለዋል። የግምገማው ተሳታፊዎች በበኩላችን ቅንጅታችንን አጠናክረን የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በበለጠ ለማረጋገጥ እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ እየተሰጠ ያለው አገልግሎት አሰጣጥ ተገልጋይ ተኮር በመሆኑ ደስተኞች ነን- ተገልጋዮች

በአገልግሎት አሰጣጥ የነበረውን ስብራት እየጠገን የደንበኞችን እርካታ የሚያረጋግጥ ፈጣን ግልፅና ምላሽ ሰጭ አገልግሎት እየሰጠን ነው-ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በልደታ ክ/ከተማ እየተሰጠ የሚገኘው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በውጤታማነቱ በተገልጋዮች ዘንድ ምገሳ እየተቸረው ነው። ተገልጋዮች እንደገለፁት በአስተዳደሩ እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን፣ ቀልጣፋና ችግር ፈች ነው ብለው አገልግሎት አሰጣጡ ተገልጋይ ተኮር እና የተገልጋይ ፍላጋጎትን የሚያሟላ በመሆኑ ደስተኞች ነን ሲሉ ገልፀዋል። የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም የነበረው የአገልግሎት አሰጣጥ በተገልጋዮች ዘንድ የቅሬታ ምንጭ ሆኖ ቆይቷል ብለው አሁን ላይ "በአዲስ ዕይታ የልደታ ከፍታ "በሚል መነሻ በአገልግሎት አሰጣጡ የነበሩ ስብራቶችን ጠግነን እርካታን የሚያረጋግጥ ፈጣን ግልፅና ምላሽ ሰጭ አገልግሎት እየሰጠን ነው በማለት ተናግረዋል። ተገልጋዮቻችን የሚያቀርቡትን ጥያቄ በተቀናጀ መንገድ ምላሽ እየሰጠን የልደታን ከፍታ የማረጋገጥ ስራ እየሰራን ነው ብለዋል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ። በየደረጃው የሚሰጠው አገልግሎት አሰጣጥ ምልልስን የሚቀንስ እርካታን የሚያረጋግጥ እንዲሆን ለማስቻል ከምንጊዜውም በላይ በትጋትና በቁርጠኝነት እየሰራን ነው ብለዋል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
የህግ ማስከበርና መልካም አስተዳደር ክላስተር ለቴክኒክ ኮሚቴዎችና ባለሙያዎች በክላስተሩ ቅንጅታዊ አሰራር ማስፈፀሚያ ማንዋል ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ::

በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በአዲሱ የተቋማት ቅንጅታዊ አሠራር የማስፈፀሚያ ማንዋል ሠነድ ለህግ ማስከበርና መልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ ፣ለክላስተር አባል ጽ/ቤቶች፣ ለቴክኒክ ኮሚቴዎች እንዲሁም ለሠራተኞች ስልጠና ተሰጥቷል። ስልጠናው ስለክላስተሩ አደረጃጀት፣ ስለ ክላስተሩ አስተባባሪ ሚና፣ የክላስተር አባል ጽ/ቤቶች ሚና እና ከቴክኒክ ኮሚቴዎች የሚጠበቅ ሃላፊነት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በተጨማሪም በክላስተሩ ዕቅድ የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በጥልቀት አንስተው ግንዛቤ ለታዳሚው ፈጥረዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በስልጠናው የተሻለ ግንዛቤ መፈጠሩን በመግለፅ የክላስተር አባል ጽ/ቤቶች ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወንጀሎችን፣ የደንብ ጥሰቶችንና ህገ ወጥ ድርጊቶችን በመከላከል የማህበረሰቡን ሰላምና ደህንነት መጠበቅ፤ ለህብረተሠቡ እየተሠሩና እየመጡ ያሉ ለውጦችን ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ በመግለፅ በዕቅዱ የተያዙ ግቦችን ለማሳካት ሁሉም ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት የጋራ መግባባት ተፈጥሯል::

image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ላይ የመስክ ምልከታ አደረገ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመው የሱፐርቪዥን ቡድን በክ/ከተማው የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎችን ከሪፖርት ባሻገር በተለያዩ ተቋማትና ወረዳዎች ላይ የመስክ ምልከታ እያካሄደ ይገኛል። ሱፐርቪዥኑ ያስፈለገበት አላማ የከተማ እና የክ/ከተማው አስተዳደር ከሀገራዊ ሪፎርሙ ጋር የተጣጣመ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የዋና ዋና ግቦች ትግበራ እና ያሉበትን ደረጃ በማየት ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል ክፍተቶችን ደግሞ ለመሙላት የሚያስችል መሆኑ የሱፐርቪዥን ቡድኑ አመራሮች ገለፃ አድርገዋል። በምልከታው በፓርቲና በመንግስት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭነት ከማረጋገጥ በተጨማሪ አጠቃላይ በአመራር ስርዓት እና ውጤታማነት፣ በራስ አቅም የተተገበሩ የልማት ስራዎች፣ አገልግሎት ከማዘመን እና የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት በማስፋት ረገድ የተሰሩ ስራዎች በምልከታው የሚረጋገጡ መሆኑ ተጠቁሟል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
"በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" የልደታ ክፍለ ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት የስራ ተሞክሮ እና ልምዱን አካፈለ።

በልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት በመገኘት የልምድ ልውውጥ ያደረገው የኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ አቻ ጽ/ቤት ሲሆን የጽ/ቤቱ ሀላፊ እና ባለሞያዎች በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል። የልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይልማ ተረፈ በልምድ ልውውጡ ላይ እንዳሉት በክ/ከተማው የመልካም አስተዳደር ስራዎች ጉዳይ እንደተቋም ተቀናጅቶ የመፍታት ችግር እንደነበር አስታውሰው በአዲስ መልክ የተዋቀረው የክ/ከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው ልዩ ትኩረት ጽ/ቤቱ በተሻለ የአፈፃፀም ቁመና ላይ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። አቶ ይልማ አያይዘው የአመራሩን የተግባር ስምሪት በማስተካከል፣ ቅንጅታዊ አሰራርን ተቋማዊ እንዲሆን በማስቻል እና ህብረተሰቡን የጉዳዩ ባለቤት በማድረግ በእቅድ የሚመራ የመልካም አስተዳደር ችግር አፈታት ተግባር ተጨባጭ ውጤት ማምጣት ተችሏል ሲሉ ለአቻ ክ/ከተማ ጽ/ቤቱ ልምዳቸውን አካፍለዋል። በቅሬታና አቤቱታ በኩል በየተቋሙና ወረዳዎች የተደራጀውን የቅሬታ ኮሚቴ ከመከታተልና መደገፍ ባሻገር ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ቅሬታዎች ለማዳመጥ የህብረተሰቡ ጋር መድረኮችን በማዘጋጀት አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲያዳምጥና የቅሬታውን አግባብነት አይቶ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ለውጥ እንደመጣበት አቶ ይልማ አክለው ገለፃ አድርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ በማድረግ በአገልግሎት ቀን ተገልጋዮችን ግልፅ በሆነ አግባብ የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የሚመለከታቸው ሴክተር ተቋማት በተገኙበት አገልግሎት ፍትሃዊና የተገልጋይን እርካታ በሚጨምር መልኩ መሰጠቱ ለውጤቱ አበርክቶ እንዳለው ተነስቷል። በልምድ ልውውጡ ላይ ተካፋይ የሆኑት የኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ እና ባለሞያዎች እንደገለፁት ከአቀባበል ጀምሮ ለተሰጣቸው ቅንነት የተሞላበት ገለፃ አመስግነው ከክ/ከተማው ያገኙት ልምድ ለቀጣይ ስራቸው እንደ ግብዓት እንደሚጠቀሙበት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

image
image
image

የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች

በልደታ ክ/ከተማ የመልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር ፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ከተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መነሻ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የለውጥ ሥራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ በብቃቱና እና በሥነ-ምግባሩ የተመሰገነ የሰው ኃይል እንዲመራ በማድረግ ለተገልጋዮቹ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በአዲስ መልክ በመለየት አደራጅቷል፡፡

በተጨማሪም በጽ/ቤት የሚሰጠው አገልግሎት የተገልጋይ ፍላጎትን ማዕከል አድርጎ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል የሚሰጡ የአገልግሎት አይነቶች፣ አገልግሎቱ የሚሰጥበት ስታንዳርድ፣ የሚሰጥበትን ቦታ እና ከተገልጋይ የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎችን በግልጽ በማስቀመጥ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሰረት ፍህታዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡና ተገልጋዮች ምን ዓይነት አገልግሎት በምን ዓይነት ደረጃ ማግኘት እንደሚገባቸው ግንዛቤ በመፍጠር በዚህም ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲኖር፣ በህዝብና መንግስት መካከል መተማመን እንዲፈጠር፣ ልማትና ዲሞክራሲ እንዲያብብ ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው፡፡ በመሆኑም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂት ለመፍታት በምናደርገው ጥረት ባለድርሻ አካላትና ህብረተሱቡ ከጽ/ቤቱ ጎን እንዲቆሙ እናሳስባለን፡፡