image
image
image
image
image

የልደታ ክፍለከተማ አስተዳደር መልካም አስተዳደር ቅሬትና አቤቱታ ፅህፈት ቤት የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።

ጥር 01/05/18, 2017
ተግባራትን በተቀናጀ ሁኔታ በመፈፀም የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመፍታት ተጠቃሚነቱን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ ተችሏል:- አቶ አሰፋ ቶላ በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት አመት የ6 ወራት የመልካም አስተዳደር ስራዎች እና የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር አፈፃፀም ተገመገመ፡፡ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው የተቋማት ተወካዮች በተገኙበት አስተዳደሩ በበጀት አመቱ 6 ወራት ያከናወናቸው የመልካም አስተዳደር ችግር አፈታት አፈፃፀም ተገምግሟል፡፡ መድረኩን የመሩት የክፍለ ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅ/ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አሰፋ ቶላ ሲሆኑ አብዛኞቹ ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ሂደት የተገኘባቸው መሆኑን ጠቅሰው በሁሉም ዘርፍ የታቀዱ ተግባራት ስኬታማ ሆነው እንዲጠናቀቁ ህብረተሰቡን በማሳተፍ መረባረብ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ መሠረታዊ የሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በቅንጅት እየፈታን የማህበረሰባችንን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ እየሰራን ነው ያሉት አቶ አሰፋ አስተዳደሩ ህገ-ወጥነትንና ብልሹ አሰራርን በመታገል በነዋሪው ዘንድ ፍትሃዊ የሆነ ተጠቃሚነት እንዲኖርም ይሰራል ብለዋል። አቶ አሰፋ አያይዘው ተግባራትን በተቀናጀ ሁኔታ በመፈፀም የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመፍታት ተጠቃሚነቱን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል። የዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጢቂ ድሪባ በበኩላቸው በተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር እና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄዎች መነሻ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ ያሉበት ደረጃ ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀው ቀሪ ስራዎችን በታቀደላቸው የጊዜ ገደብ መሰረት በማጠናቀቅ መረባረብ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ይልማ ተረፈ በአፈፃፀም መድረኩ ላይ እንዳሉት በባለፋት 6 ወራት የተለዩትን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመርህ እና በአሰራር በመፍታት የአስተዳደሩን ለህዝብ ጥያቄ ቅድሚያ ሰጥቶ የመመለስ መርህ በሚገባ አሳክተናል ብለዋል። የግምገማው ተሳታፊዎች በበኩላችን ቅንጅታችንን አጠናክረን የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በበለጠ ለማረጋገጥ እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች